Apr 2024

የማሽነሪ አምራች ኢንዱስትሪ ኢኮኖሚያዊ ሽግግሩን ውጤታማ ከማድረግ በተጨማሪ ለዜጎች የስራ ዕድል ፈጠራ ዓይነተኛ ሚና አለው ተባለ፡፡

ሚያዚያ7/2016 ዓ.ም የዘርፉን ችግር መፍታት ዓላማው ያደረገ የማሽነሪ አምራች ኢንዱስትሪዎች ሀገራዊ ዕድሎችና ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ ልዩ የምክክር መድረክ ተካሂዷል፡፡

የግብርና ምርቶች ላይ እሴት በመጨመር ወደ ውጭ በመላክ የአምራች ኢንዱስትሪውን ገበያ ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ነው (አቶ ሐሰን ሙሐመድ)

አዲስ አበባ 04/08/2016 ዓ.ም (ኢ.ሚ) የተቀናጁ አግሮ-ኢንዱስትሪ ፓርኮች አሠራርና ዘላቂነት በኢትዮጵያ ፕሮጀክት ላይ ትኩረት ያደረገ የፌደራል፣ክልል ከፍተኛ አመራሮች እና የልማት አጋሮች የተገኙበት ውይይት ተካሄደ፡፡

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ረቂቅ ፖሊሲ አፀደ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 29ኛ መደበኛ ስብሰባ ውሳኔ ካስተላለፈባቸው ጉዳዮች አንዱ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ረቂቅ ፖሊሲ መሆኑ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ አመላክቷል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ አመራሮችና ሰራተኞች በሳይንስ ሙዚየም በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅ ሚኒስቴር የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ስታርታ አፕ ኤግዚቪሽ ጎበኙ

ሚያዚያ 03/2016 ዓ.ም (ኢሚ) በኤግዚቪሽኑ በዲጂታል፣ በግብርና፣ በሃይል፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በማንፋክቸሪንግ እና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ የመጀመርያ ደረጃ ላይ የሚገኙ ፣የመጀመርያ ደረጃውን የተሻገሩ፣ ወደ ገበያ መቀላቀል ደረጃ ላይ የደረሱ ስታርት አፖች ስራዎቻቸውን ተመልክተዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ድጋፍ አደረገ

ሚያዚያ1/2016 ዓ.ም (ኢ.ሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የአየር ንብረት ለውጥ ፕርፎርማንስ ፕሮጀክት በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አሚባራ ወረዳና በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሽንሌ ወረዳ ለሚገኙ የፕሮጀክቱ የሳይት ሰራተኞች እና ለአካባቢው ማህበረሰብ ድጋፍ አድረገ።

"የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን ለመገንባት እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ውጤት እያመጣ ነው" (አቶ መላኩ አለበል)

መጋቢት 30/2016ዓ.ም (ኢ.ሚ) ዶዳይ ማኑፋክቸሪንግ ያመረታቸውን የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክሎች አስመረቀ። በምረቃው መድረክ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ እንደገለፁት የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክሎቹ እንደሀገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ትልቅ ሚና አላ

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ከአፍሪካ ህብረት ንግድና ኢንዱስትሪ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጋር ተወያዩ።

መጋቢት 30/2016 ዓ.ም (ኢ.ሚ)የኢፌድሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚንስትር አቶ መላኩ አለበል ከአፍሪካ ንግድና ኢንዱስትሪ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሚስተር አልበርት ሙቻንጋ ጋር አብሮ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

የሀገር ዉስጥ ምርትን መጠቀም አርበኝነት ነዉ /ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)/

መጋቢት 29/2016ዓ.ም (ኢ.ሚ)የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ ታምርት ተነሳሽነት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ስኬት እያስመዘገበ ነው ያሉት ሚንስትሩ የሀገር ዉስጥ ምርትን መጠቀም አርበኝነት እንደሆነም ገልጸዎል።

ለቱሪዝም ዘርፍ የሚውሉ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት ስኬታማ ሥራ እየተከናወነ ነው (አቶ ተመስገን ጥሩነህ)

መጋቢት 29/2016(ኢ.ሚ) ለቱሪዝም ዘርፍ የሚውሉ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት ስኬታማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ መንግሥት ተኪ ምርቶችን ለማስፋት ያስቀመጠው አቅጣጫ ለማስፈጸም በትኩረት እየተ

ለቱሪዝም ዘርፉ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ፣ለዜጎች ዘላቂ የስራ እድል በመፍጠር ረገድ አምራች ኢንዱስትሪ ትልቅ ሚና እንዳለው ተገለፀ።

መጋቢት 28/2016ዓ.ም (ኢ.ሚ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ የተመራ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች ልዑክ የሳፋሪ ተሸከርካሪዎችን ማምረቻ ኢንዱስትሪዎችን የሥራ እንቅስቃሴን ጎብኝቷል።

በም/ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ የተመራ ልዑክ የቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ማምረቻ ኢንዱስትሪን ጎበኙ

መጋቢት 28/2016ዓ.ም(ኢ.ሚ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ የተመራ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች ልዑክ የቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ማምረቻ ኢንዱስትሪ የሥራ እንቅስቃሴን ጎብኝቷል።

በአምራች ኢንዱስትሪዎች የህፃናት ማቆያ ማዕከላት መኖር ለኢንዱስትሪው ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው (አቶ ሀሰን መሐመድ)

መጋቢት25/2016 ዓ.ም በይርጋለም ጋርመንት እና ኢትዮኢምፓክት አምራች ኢንዱስትሪዎች ውስጥ የተገነቡ የህፃናት ማቆያ ማዕከላት የምረቃ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል፡፡

የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የጋራ ውጤት፣ የወል እውነት፣ የዚህ ትውልድ ደማቅ አሻራ፣ ለቀጣይ የልማት ሥራዎች መንደርደሪያ ዓቅም ነው::

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በዓባይ ወንዝ ላይ ለዘመናት ለነበረው የሕዝብ ቁጭት ምላሽ የሰጠ፣ የሉዓላዊነት መገለጫ እና የልማታችን ብርሃን በመኾን ከመጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት 12 ዓመታት ለግድቡ ግንባታ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ያለ ልዩነት በጉልበት፣ በእውቀት፣ በተፋሰስ ልማት ጥበቃ ሥራ፣ በፋይናን

የሕዳሴው ግድብ ሀገራዊ ኢኮኖሚን በማነቃቃት የልማት መሠረት ሆኖ በማገልገል ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ አለው።

የግድቡ ግንባታ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ በማነቃቃት የልማት መሠረት ሆኖ ከማገልገል በተጨማሪም በማህበራዊ ዘርፉም እንደ ሀገር የተያዙ ውጥኖችን በማሳካት፣ በዲፕሎማሲው ዘርፍም ተሰሚነትን ከፍ ለማድረግ፣ሀገራችን ያዘችውን በቀጠናው አብሮ የመልማትና ከኮረቤት ሀገሮች ጋር በኢኮኖሚ የመተሳሰር ዕቅዶችን በማሳካት ረገድ ትልቅ ሚ

የግድቡ መጠናቀቅ በኃይል እጥረት ወደኋላ የቀሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲያንሰራሩ ያደርጋል” (አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ)

መጋቢት 25/2016 ዓ.ም (ኢ.ሚ) የዓባይ ግድብ መጠናቀቅ በኃይል አቅርቦት ላይ ያለውን ችግር በመፍታት ወደኋላ የቀሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲያንሰራሩና እንዲጠናከሩ እንደሚያደርግ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀⵆ

የዓለም ባንክ ም/ፕሬዝደንት ሊሳ ሮሰን በአዲስ አበባ የሚገኙ አምራች ኢንተርፕራይዞችን ጎበኙ

መጋቢት 24/2016 ዓ.ም (ኢሚ) የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የግብዓትና መሰረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ሀሰን መሐመድ፣ የዓለም ባንክ ምክትል ፕሬዘዳንት፣ የዓለም ባንክ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በዓለም ባንክ እየተደገፉ ያሉ አነስተኛና መካከለኛ አም

Mar 2024

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ከጃፓን አምባሳደር ጋር በአምራች ኢንዱስትሪ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ውይይት አደረጉ

መጋቢት19/2016 ዓ.ም (ኢ.ሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ከጃፓን አምባሳደር ሺባታ ሂርኖር ጋር በአምራች ኢንዱስትሪ እና እንደ ሀገር ባሉ የኢንቨስትመንት አማራጮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

ለአምራች ኢንዱስትሪ ባለሙያዎች የኢንዱስትሪ የሀይል አጠቃቀም ስርዓትን ለማዘመን የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ

መጋቢት19/2016 ዓ.ም (ኢ.ሚ)የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለአምራች ኢንዱስትሪ ባለሙያዎች የኢንዱስትሪ የሀይል አጠቃቀም ስርዓትን ለማዘመን የሚያስችል ስልጠና ሰጥቷል፡፡

በተለያየ ዘርፍ ከተሰማሩ የቻይና አምራች ድርጅቶች ጋር የኢንዱስትሪ ምቹ ሁኔታዎችና በዘርፉ ያሉ ዕድሎች ላይ ያተኮረ ዉይይት ከኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አቶ ዳንኤል ኦላኒ ጋር አድርገዋል።

በተለይ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብት የታደለች፣ የሰለጠነና ሊሰለጥን የሚችል የኢንዱስትሪ የሰዉ ሀይል ያላት፣ በመንግስትና በግል ዘርፉ የተገነቡ ኢንዱስትሪ ፓርኮች መኖራቸው፣ በመልካ ምድራዊ አቀማመጥና ምቹ የአየር ሁኔታ መኖሩንም አማካሪው ገልጸው በዘርፉ ፍላጎት ያላቸው ባለሀብቶች እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የፌደራል መንግስት የድጋፍና ክትትል ቡድን በሶማሊ ክልል ያደረጉትን የምልከታ ሪፖርት ለክልሉ መንግስት አቀረበ

የመጋቢት 14 /2016 ዓ.ም(ኢ.ሚ) በኢፌዲሪ የግብርና ሚኒስትሩ ዶ/ር ግርማ አመንቴ የተመራዉ የድጋፍና ክትትል ቡድን በሶማሊ ክልል ዞኖችና ወረዳዎች ያካሄዱት የአገልግሎት አሰጣጥ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች የምልከታ ሪፖርት ለክልሉ መንግስት አቅርቧል።

በህንድ እና በኢትዮጵያ መካከል እያደገ የመጣውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር ማጠናከር ያስፈልጋል (አቶ ሀሰን መሀመድ)

መጋቢት13/2016ዓ.ም (ኢ.ሚ) በህንድ እና በኢትዮጵያ መካከል እያደገ የመጣውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማጠናከር የሚረዳ የውይይት መድረክ ተካሄዷል፡፡ ህንድን ከኢትዮጵያ ጋር ያገናኘው የኬሚካል ገዥና ሻጮች የውይይት መድረክ ላይ የኢንዱስትሪ ሚንስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን ሙሀመድ የተደረገው ውይይት በሁለቱ ሀገራት መ

የተቋምን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመንና ለማሻሻል የሚያስችል ስልጠና በካይዘን የልህቀት ማዕከል ተሰጠ

መጋቢት12/2016 ዓ.ም (ኢ.ሚ) ስልጠናው በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በካይዘን ልህቀት ማዕከል ለሰራተኞችና ለተገልጋዮች ምቹና ሳቢ የስራ ቦታ በመፍጠር የግብዓትና የጊዜ ብክነት በማስወገድ፣ወጪን በመቀነስ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን በማሳደግ ለአገልግሎት ሰጪውና ተቀባዩ የስራ አካባቢ ምቹ ማድረግ ዋና አለማ ያደረገ ነው

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን ሙሀመድ በኢትዮጵያ ያለዉን የገበያ አማራጭና ፍላጎት ግዢ ለማጥናት ከመጡ የዝምባቡዌ trade promotion agency የስራ ሃላፊዎች ጋር በሁለቱ ሀገራት የኢንቨስትመንት ዕድሎች ዙሪያ ዉይይት አድርገዎል።

"በአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጠና ስምምነት ዉስጥ የሀገራት ሁለትዮሽ ግንኙነት የኢንቨስትመንት ትስስሩን ይበልጥ እንደሚያጠናክረዉ " አቶ ሀሰን ሙሀመድ ገልጸዎል።

በአቶ መላኩ አለበል የተመራ የሱፐርቪዥን ቡድን በሠመራ የሚገኙ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትንና የኢንዱስትሪዎችን የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

መጋቢት11/2016ዓ.ም(ኢ.ሚ) በሠመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ያለውን የነዋሪዎች የመልማት ፍላጎት ሊያሳካ የሚችል የገቢ አሰባሰብና መሠረተ ልማት መሠራት አንዳለበት የኢንዱስትሪ ሚኒስትርና የሱፐርቪዥን ቡድኑ መሪ አቶ መላኩ አለበል ገለፁ።

በአቶ መላኩ አለበል የተመራ የፌዴራል አመራሮች የሱፐርቪዥን ቡድን በአፋር ክልል የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ጉብኝተዎል።

መጋቢት 11/2016ዓ.ም(ኢ.ሚ) በኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የተመራ የፌዴራል አመራሮች የክትትልና ድጋፍ ቡድን በአፋር ክልል ምልከታ አድርገዎል። ቡድኑ የክትትልና የድጋፍ ስራውን ከመጋቢት 06 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ከአቶ አወል አርባና ከክልሉ ካቢኔ አባላት ጋር ባካሄደ

በግብርና ሚኒስትር ዶ/ር ግርማ አመንቴ የተመራ የድጋፍና ክትትል ልዑክ ሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ሽንሌ ወረዳ የሚገኙ የስቦንጅ እና የፕላስቲክ ፍብሪካ እንዲሁም የከብት እና የግመል እርባታን ጎብኝተዎል።

መጋቢት 10/2016ዓ.ም(ኢ.ሚ) በግብርና ሚኒስትር ዶ/ር ግርማ አመንቴ የተመራ የድጋፍና ክትትል ልዑክ ሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ሽንሌ ወረዳ የሚገኙ የስቦንጅ እና የፕላስቲክ ፍብሪካ እንዲሁም የከብት እና የግመል እርባታን ጎብኝተዎል።

በገንዘብ ሚንስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የድጋፍና ክትትል ልዑክ በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ ሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክና ከፓርኩ ውጭ የሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል ።

መጋቢት 9/07/2016(ኢ.ሚ) በገንዘብ ሚንስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የድጋፍና ክትትል ልዑክ በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ ሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክና ከፓርኩ ውጭ የሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል ። በጉብኝታቸው ወቅትም በኢንዱስትሪው ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ጠንካራ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በማሳሰብ በ

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚንስትር ደኤታ አቶ ሀሰን ሙሀመድ በአቶ ጆናታን ሰይድ የተመራው አሊያንስ ፎር ኤ ግሪን ሪቮሊዩሽን ኢን አፍሪካ (AGRA) ከፍተኛ ልዑካን ቡድንን ተቀብሎ ተወያይቷል።

የግብርና እና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎችን ከኢትዮጵያ የልማት ግቦች ጋር በማያያዝ ማጠናከር ላይ ያተኮረ ዉይይት አድርገዎል። አርሶ አደሮችንና ኢንዱስትሪዎችን ማስተሳሰር፣ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ እና የአቅም ግንባታ ውጥኖችን ማሳደግን ጨምሮ የትብብር እድሎች ላይ ተወያይተዋል።

የአምራቾችን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የመንግስትና የግል ዘርፍ የጋራ ምክክር ወሳኝነት አለው (የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚ/ዴኤታ አቶ ሀሰን ሙሐመድ)

መጋቢት 9/2016 ዓ.ም (ኢሚ) በኢትዮጵያ የዱቄትና የዱቄት ውጤቶች አምራቾች ዘርፍ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች እና መፍትሄ አቅጣጫ ላይ ያተኮረ የመንግስትና የግል ዘርፍ የጋራ ምክከር መድረክ ተካሄደ፡፡ በኢትዮጵያ ዱቄትና የዱቄት ውጤቶች አምራቾች ማህበር እና የጀርመን የልማት ትብብር (GIZ) ጥምረት በተዘጋጀው የ

በግብርና ሚኒስትር ዶ/ር ግርማ አመንቴ የተመራ ልዑክ ሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ሽንሌ ወረዳ የሚገኙ ፍብሪካዎችን ጎበኙ የቪታ የታሸገ ውሃ ፋብሪካ እና ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ያለ የማርብል ፋብሪካ ተጎብኝተዋል፡፡ ይከታተሉን📷 #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት

በግብርና ሚኒስትር ዶ/ር ግርማ አመንቴ የተመራ ልዑክ ሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ሽንሌ ወረዳ የሚገኙ ፍብሪካዎችን ጎበኙ የቪታ የታሸገ ውሃ ፋብሪካ እና ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ያለ የማርብል ፋብሪካ ተጎብኝተዋል፡፡ ይከታተሉን #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት

በገንዘብ ሚንስትሩ በክቡር አቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የድጋፍና ክትትል ልዑክ በታላቅ ድምቀት በሀዋሳ ከተማ ሲካሄድ የነበረውን ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት ኤግዚቭሸንና ባዛር ጉብኝት አደረጉ ! ይከታተሉን📷 #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት

በ7/07/2016 በገንዘብ ሚንስትሩ በክቡር አቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የድጋፍና ክትትል ልዑክ በታላቅ ድምቀት በሀዋሳ ከተማ ሲካሄድ የነበረውን ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት ኤግዚቭሸንና ባዛር ጉብኝት አደረጉ ! ይከታተሉን #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት

የአገር ውስጥ ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በመሰማራት ለሀገር ኢኮኖሚ ማደግ የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት ይጠበቅባቸዋል(ክቡር አቶ ሀሰን መሐመድ)

መጋቢት 5/2016 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት በዘርፉ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮች፣ መልካም አጋጣሚዎችና ማበረታቻዎችን ለሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በማስተዋወቅ ለዘርፉ ዕድገት የሚያበረክተውን ተሳትፎና ሚና ለማሳደግ ዓላማው ያደረገ የአምራች ኢንዱስትሪ የኢንቨስትመንት የ

ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራርና ሰራተኞች ሀገራዊ የዘርፎች 6 ወር እቅድ አፈጸጸም ላይ ውይይት አደረጉ ፡

መጋቢት 04/2016 ዓ.ም(ኢሚ) በቀረበው ሀገራዊ የዘርፎች 6 ወር እቅድ አፈጸጸም ከተሳታፊዎች ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ አሁን ያለበትን ደረጃ እና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ዙሪያም ውይይት ተካሄዷል፡፡

የኢትዮ-ጣሊያን ኢንቨስትመንት ትስስር የሚያጠናክር ውይይት ተካሄደ

መጋቢት 03/2016 ዐ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ ከጣልያን ልማት ትብብር ዋና ዳይሬክተር ስቲፋኖ ጋቲ እና ልዑካቸው ጋር የሁለቱን አገራት የኢንቨስትመንት ትስስር በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ ኢንዱስትሪያላዜሽንና የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር የመንግስታችን የኢኮኖሚ አጀ

የፕሮሶፒስ ጁሊፍሎራ መጤ አረም ፕሮጀክት አፈፃፀም ሂደት እየተገመገመ ነው

መጋቢት 03/2016 ዓ.ም (ኢሚ) በአየር ንብረት ለውጥ ፐርፎስማንስ ፕሮጀክት በፐሮሶፒስ ጁሊ ፍሎራ መጤ አረም (ወያኔ አረም) የተወረሩ የእርሻና የግጦሽ መሬቶችን በመመንጠር የመጤ አረሙን አማራጭ የኃይል ምንጭ ሆኖ እንዲያገለግልና መሬቶችን መልሶ ለሰብል ምርት እንዲውሉ ማድረግ አላማ በማድረግ ወደ ስራ የገባው ፓይ

በሴቶች ላይ ኢንቨስት ማድረግ እድገትን ያፋጥናል"

አዲስ አበባ የካቲት 29/2016 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከኢንተርናሽናል ሌበር ኦርጋይኔዜሽን ጋር በመተባበር በአምራች ኢንዱስትሪዎች ዉስጥ በተለይም በሴቶች በሚመሩ ኢንተርፕራይዞች የሴቶች አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ እና ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር የተጀመረው ፕሮግራም ውጤት እያመጣ መሆኑን የኢንዱ

ሴቶች በሁሉም ዘርፍ የሚገጥሟቸውን ችግሮችና መሰናክሎች በማለፍ የራሳቸውን አቅም ማብቃት እንዲችሉ ያስፈልጋል

አዲስ አበባ የካቲት 29/2016 ዓ.ም (ኢሚ) በኢትዮጵያ ለ48ተኛ ጊዜ፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ113ኛ ጊዜ "ሴቶችን እናብቃ፣ ልማት እና ሰላምን እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ያለውን ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን (ማርች8) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከኢንተርናሽናል ሌቤር ኦርጋኔዝሽን ጋር በመተባበር እያከበረ ነው

በቆዳው ኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የውይይት መድረክ ተካሄደ

ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የካቲት 27/2016 ዓ.ም በቆዳ ኢንዱስትሪው ዘርፍ በሚታዩ ወቅታዊ ችግሮች ዙሪያ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት አወያይቷል፡፡ በመርሀግብሩ የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች፣ በዘርፉ የተሰማሩ የፋብሪካ ባለሀብቶች፣ከብሔራ ንግድ ባንክ፣ከአካባቢጥበቃ ባለስልጣንና ከገቢዎች ሚኒስቴር የተውጣጡ ተወካዮች

የ2016 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሄደ

የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ኢሚ) በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ኢንዱስትሪያሊዜሽን ለሃገር እድገት እና ህልውና ካለው ቁልፍ ሚና አንጻር የተቀረጸው “የኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ በኢትዮጵያ የተሰሩ ምርቶችን ለአለም አቀፍ ተመልካቾች የማስተዋወቅ ትልቅ ሚና እንደነበረው የኢንዱስትሪ ሚንስትር አቶ መላኩ አለበል ገልፀዋል።

የአድዋ የብዝሃ ማንነታችን መሰረት ነው (ክቡር አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ)

የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ኢሚ) የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት አመራሮችና ባለሙያዎች 128ኛውን የአድዋ ድል በዓል አከበሩ የእድገትና ተወዳዳሪነት ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ ክብረ በዓሉን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት አድዋ ቅድመ አያቶቻችን ያወረሱን የ